በትግራይ ከሥራ ቦታ፣ ከመንገድ እና ከመኖሪያ ቤት እየተካሄደው ያለው አፈሳ የፈጠረው ስጋት

📌 Diğer 📰 Ethiopia 🕐 3 saat önce
በትግራይ ከሥራ ቦታ፣ ከመንገድ እና ከመኖሪያ ቤት እየተካሄደው ያለው አፈሳ የፈጠረው ስጋት

በትግራይ ክልል የተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ ወጣቶች ከሥራ ቦታቸው፣ ከመዝናኛ ስፍራ እንዲሁም ከሕዝብ ትራንስፖርት ላይ በግዳጅ ተወስደው ወደ ተለያዩ ካምፖች መላካቸውን ለቢቢሲ ትግርኛ ተናገሩ። የትግራይ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ በትግራይ "የተመለመሉ" ወጣቶችን ለሠራዊት እያሰለጠነ መሆኑን ለቢቢሲ ትግርኛ ገልጾ የምልመላው ሂደት ግን "በክልሉ መንግሥት እንደሚፈፀም" ተናግሯል። ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች ኢትዮጵያ በበኩሉ የትግራይ ፀጥታ ኃይሎች በክልሉ መጠነ ሠፊ አፈሳ እና የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ እያካሄደ መሆናቸውን በመጥቀስ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።

የትግራይ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ በትግራይ "የተመለመሉ" ወጣቶችን ለሠራዊት እያሰለጠነ መሆኑን ለቢቢሲ ትግርኛ ገልጾ የምልመላው ሂደት ግን "በክልሉ መንግሥት እንደሚፈፀም" ተናግሯል።

ቢቢሲ ያነጋገራቸው በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ ወጣቶች ከሥራ ቦታቸው፣ ከመዝናኛ ስፍራ እንዲሁም ከሕዝብ ትራንስፖርት ላይ በግዳጅ ተወስደው ወደ ተለያዩ ካምፖች መላካቸውን ተናግረዋል።

ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች ኢትዮጵያ በበኩሉ የትግራይ ፀጥታ ኃይሎች በክልሉ መጠነ ሠፊ አፈሳ እና የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ እያካሄደ መሆናቸውን በመጥቀስ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጊቶቹ ይፈጸምባቸዋል በሚል ከዘረዘራቸው አካባቢዎች መካከል፣ ሰሜን ምሥራቅ ዞን፣ ማዕከላዊ ዞን እና ምሥራቃዊ ዞን ይገኙበታል።

ለሁለት ዓመታት የተካሄደውን ጦርነት ባስቆመው የፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት የተቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር በማፍረስ ከጦርነቱ በፊት የነበረው የክልሉ ምክር ቤት ሥልጣን ከያዘ በኋላ በህወሓት መሪዎች እና በፌደራል መንግሥቱ መካከል ውጥረት ተፈጥሯል።

ተመልሶ ሥራ የጀመረው ፈርሶ የነበረው የትግራይ ክልል ምክር ቤት ሕጋዊ የፓርቲ ዕውቅናው የተሰረዘበትን የህወሓት ሊቀመንበር ደብረፂዮን ገብረ ሚካኤልን የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ የሾመ ሲሆን፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ያሉበት ሁኔታ አስካሁን በይፋ አይታወቅም።

በዚህም የተነሳ በክልሉ ሌላ ዙር ግጭት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚል ስጋት የተፈጠረ ሲሆን፣ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ እየተካሄደ መሆኑን ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የመብት ድርጅት በመግለጫቸው አመለክተዋል።

በተጨማሪም በደብረፂዮን የሚመራው የክልሉ መንግሥት በቅርቡ ይፋ ያደረገው ረቂቅ ሕግ ዕድሜያቸው እና የጤና ሁኔታቸው የሚፈቅድላቸው ማንኛውም የትግራይ ተወላጆች የክልሉ መንግሥት የሚያቀርበውን "የክተት ጥሪ ተቀብሎ የመሳተፍ ብሔራዊ ግዴታ" እንዳለባቸው ይደነግጋል።

ይህንን የማይቀበል ማንኛውም ሰው "ከ10,000 እስከ 50,000 ብር ተቀጥቶ ግዴታውን እንዲፈጽም ይደረጋል" የሚል አንቀጽ በረቂቅ ሕጉ ላይ ተቀምጧል።

የትግራይ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ህወሓት በክልሉ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ እያደረገ መኾኑን በመግለጽ መግለጫዎችን አውጥተዋል።

ዓረና ትግራይ እንዲሁም ስምረት ፓርቲ ህወሓት የቀድሞ ተዋጊዎችን፣ ሚሊሻዎችን እና የትግራይ ወጣቶችን በግዳጅ ለወታደራዊ ሥልጠና በመመልመል በማፈስ ወዳልታወቁ ካምፖች እየወሰደ ነው ሲሉ ባወጡት መግለጫ ከስሰዋል።

ቢቢሲ ትግርኛ በታጣቂዎች በአስገዳጅ ለውትድርና የታፈሱ ሰዎችን፣ ከወታደራዊ ማሠልጠኛ ያመለጡ ወጣቶችን እና ቤተሰባቸውን አነጋግሯል።

ነገር ግን የአካባቢ መስተዳድሮች እና የሰላም እና ፀጥታ ጽሕፈት ቤቶች ግን እየተካሄደ ያለውን ወታደራዊ አፈሳ አስተባብለዋል።

በዓድዋ ከተማ የሚኖረው የአንዲት ልጅ አባት የሆነው ተስፋይ ገብረእግዚአብሄር በማዕከላዊ ዞን በሚገኘው አሕሰአ ወረዳ ልዩ ስሙ ዓዲፍታው በሚባል ቀበሌ በባህላዊ መንገድ ወርቅ በማውጣት ይተዳደራል።

በዚህ በወርቅ ማውጫ አካባቢ የተሰማሩ ወጣቶች ቀን ላይ ወርቅ ሲያወጡ ይውሉ እና ሌሊቱን በዚያው አካባቢ ትንሽ ድንኳን ዘርግተው ያድራሉ።

ግንቦት 13/2018 ዓ.ም. ከማለዳው 11፡30 ወደ ሥራቸው ለመሄድ ከእንቅልፋቸው ሲነሱ ዙሪያቸውን በታጣቂዎች እና በፖሊሶች ተከብቦ 180 ወጣቶች ዓዲፍታው ወደሚባል ትምህርት ቤት ተወስደው በአንድ ክፍል ቤት ተቆልፎባቸው አደሩ።

ለደኅንነቱ በመስጋት ስሙ እንዳይገለጽ የጠየቀ እና ከታፈሱት ወጣቶች መካከል አንዱ በማግስቱ ግንቦት 14/2018 ዓ.ም. ሲቪል የለበሱ እና የታጠቁ ሰዎች በመምጣት "ወደ ግንባር፣ ወደ ትጥቅ ትግል እንድንሄድ እንዳፈሱን ነገሩን" ይላል።

ወጣቶቹ በሦስት አውቶብሶች ተጭነው በማዕከላዊ ዞን ነበለት አቅራቢያ ወደ ሚገኘው ሰጉሕ ወደሚባል ወታደራዊ ማሠልጠኛ እንደተወሰዱ ቢቢሲ ያነጋገራቸው ግለሰቦች አስረድተዋል።

ማርያም ሸዊቶ ከሚባል ቀበሌ እንደደረሱ ተስፋይ ከአፈሳው እና የሚጠብቀው ወታደራዊ ሥልጠና ለማምለጥ ከመኪና ከዘለለ በኋላ ጭንቅላቱ ላይ ከባድ ጉዳት ደርሶበት ሆስፒታል እንደሚገኝ ወንድሙ ለቢቢሲ ተናግሯል።

ወጣቱ የጭንቅላት ቀዶ ሕክምና ቢደረግለትም ተደርጎለት "እስከ አሁን ራሱን እንደሳተ ነው። መናገርም አይችልም...ሰባተኛ ቀኑ" ሲል ወንድሙ ገልጿል።

የአሕሰአ ወረዳ ሰላም እና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ገብሩ "ይህ ለራስ ፖለቲካዊ ጥቅም፣ ሕዝብ ለማደናገር እና ችግር ለመፍጠር ካልሆነ በስተቀር በዚያ ደረጃ የተካሄደ አፈሳ የለም" በማለት ጉዳት የደረሰበትም ሰው እንደሌለ አስተባብለዋል።

በተመሳሳይ ቀን ግንቦት 17/2018 ዓ.ም. በዓብይ ዓዲ ከተማ አቅራ

📌 Kaynak

Bu haber XML kaynağından derlenmiştir. Tamamı için orijinal habere gidin.

Orijinal haberi oku →
📱
News AI World — Mobil uygulama
Bu haberleri 45 dilde, anlık çeviriyle cebinde. Erken erişim için Gmail adresini bırak.
← Tüm haberlere dön