ትራምፕ ከኢራን ጋር የተስማሙባቸውን ነጥቦች ከአርብ በፊት ይፋ ሊያደርጉ ይችላሉ ተባለ

📌 Diğer 📰 Ethiopia 🕐 3 saat önce
ትራምፕ ከኢራን ጋር የተስማሙባቸውን ነጥቦች ከአርብ በፊት ይፋ ሊያደርጉ ይችላሉ ተባለ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነቱን ለማቆም የተስማሙባቸውን ነጥቦች ከአርብ በፊት ይፋ ሊያደረጉ እንደሚችሉ ምክትላቸው ጄዲ ቫንስ ተናገሩ። ትራምፕ ስምምነቱ መፈረሙን ተናግረው የነበረ ሲሆን አርብ በስዊዘርላንድ የሁለቱ አገራት ልዑካን በአካል ተገናኝተው ፊርማቸውን እንደሚያኖሩ እየተነገረ ነው። ጄዲ ቫንስ የመግባቢያ ሰነዱ “አንድ ገጽ ከግማሽ” እና “በጣም ጥቅል” ሰነድ መሆኑን ተናግረዋል።

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነቱን ለማቆም የተስማሙባቸውን ነጥቦች ከአርብ በፊት ይፋ ሊያደረጉ እንደሚችሉ ምክትላቸው ጄዲ ቫንስ ተናገሩ።

ትራምፕ ስምምነቱ መፈረሙን ተናግረው የነበረ ሲሆን አርብ በስዊትዘርላንድ የሁለቱ አገራት ልዑካን በአካል ተገናኝተው ፊርማቸውን እንደሚያኖሩ እየተነገረ ነው።

ጄዲ ቫንስ የመግባቢያ ሰነዱ “አንድ ገጽ ከግማሽ” እና “በጣም ጥቅል” ሰነድ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራጋቺ ከአሜሪካ ጋር ዘላቂ ሰላም ላይ ለመድረስ የሚደረገው አዲሱ ዙር ውይይት በዚያው ዕለት ስዊትዘርላንድ ውስጥ እንደሚጀመር ተናግረዋል።

ለቡድን ሰባት አገራት ስብሰባ ፈረንሳይ የሚገኙት ዶናልድ ትራምፕ ትናንት ማክሰኞ ዕለት ከግብጽ፣ ኳታር እና ዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ መሪዎች ጋር ተገናኝተው በኢራን ዙሪያ መክረዋል።

ሰኞ ዕለት ትራምፕ ከፈረንሳዩ ፕሬዚፈዳንት ኢማኑዔል ማክሮን ጋር ሲነጋገሩ “ተፈርሟል ብዬ ስነግራችሁ በጣም ደስተኛ ነኝ፤ ስምምነቱ ተፈርሟል” ብለው ነበር።

የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ስምምነቱ የትራምፕ፣ የምክትላቸው ቫንስ እና የኢራን የፖርላማ አፈ ጉባዔ ሞሐመድ ባጋር ጋሊባፍ ኤሌክትሮኒክስ ፊርማ ተቀምጦበታል ብለዋል።

በዚህ ሳምንት የስምምነቱ ዝርዝር ነጥቦች ላይ እንዲሁም በኢራን ኒውክሌር ፕሮግራም ላይ መነጋገር ይጀመራል ተብሏል።

ኢራን ላይ የተጣሉትን ማዕቀቦች ለማንሳት ወይም እንዳይንቀሳቀሱ የተደረጉ ሃብቶቿን ለመልቀቅ ኢራን ለስምምነቱ ያላት ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል።

ቫንስ ለኤንቢሲ እንደተናገሩት በስምምነቱ መሠረት የኒውክሌር ተቆጣጣሪ ወደ ኢራን መግባት አለበት ብለዋል።

“የስምምነቱ አንኳር ነጥቦች ከሆኑት መካከል አንዱ [ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኤነርጂ ኤጀንሲ] እና ዩናይትድ ስቴትስ በከፍተኛ ሁኔታ ተብላልቶ የተቀመጠውን ዩራኒየም እንድታስወግድ እንደሚደግፉ በግልጽ ተቀምጧል።”

ትራምፕ የስምምነቱ ዝርዝር ነጥቦች አርብ ዕለት ከተፈረሙ በኋላ ይፋ ይሆናሉ ብለው የነበረ ቢሆንም ቫንስ ግን ከፎክስ ኒውስ ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ ወቅት ከዚያ በፊት ይፋ ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል።

ቫንሰ ከሲኤንኤን ጋር በነበራቸው ቆይታም ሰነዱ ጥቅል መሆኑን እና በርካታ ዝርዝር ጉዳዮች ወደፊት በሚደረጉ ንግግሮች መግባባት ላይ ሊደረስባቸው ይገባል ብለዋል።

📌 Kaynak

Bu haber XML kaynağından derlenmiştir. Tamamı için orijinal habere gidin.

Orijinal haberi oku →
📱
News AI World — Mobil uygulama
Bu haberleri 45 dilde, anlık çeviriyle cebinde. Erken erişim için Gmail adresini bırak.
← Tüm haberlere dön