አሜሪካ እና ኢራን ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ የተኩስ አቁሙ ማብቃቱን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ተናገሩ
የአሜሪካ በኢራን ውስጥ ጥቃቶችን ከፈጸመች እና ኢራን በአካባቢው ያሉ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች ላይ የአጸፋ እርምጃ መውሰዷን ካሳወቀች በኋላ በሁለቱ ወገኖች መካከል የነበረው የተኩስ አቁም ማብቃቱን የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስታወቁ።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ተፈረመው ጊዜያዊ ስምምነት “አብቅቷል” ማለታቸውን ተከትሎ በዓለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ በስድስት በመቶ ጨመረ።
ትራምፕ ይህንን ከማለታቸው አስቀድሞ የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከ76 ዶላር በታች ሲሸጥ ነበር። ከፕሬዝዳንቱ ንግግር በኋላ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከስድስት በመቶ በላይ በመጨመር 78.73 ዶላር መድረሱን ሮይተርስ ዘግቧል።
የአሁኑ ጭማሪ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ከተመዘገበው ከፍተኛው እንደሆነም ተገልጿል። በኢራን ጦርነት ምክንያት ዋጋው አሻቅቦ ወራትን ያስቆጠረው ነዳጅ፤ ሁለቱ አገራት ጦርነቱን ለመቋጨት የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ ቅናሽ አሳይቶ ነበር።
ይሁን እንጂ ከትናንት ሌሊት አሜሪካ የኢራን ይዞታዎችን ከደበደበች በኋላ መጨመር ጀምሯል። አሜሪካ ጥቃቱን የፈጸመችው በሆርሙዝ ወሽመጥ ሲጓዙ የነበሩ ሦስት ነዳጅ ጫኝ መርከቦች በመመታታቸው እንደሆነ ገልጻለች።
ለዋሽንግተን ጥቃት አጸፋ የሰጠችው ኢራን በበኩሏ፤ በባሕረ ሰላጤው የሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሠፈሮችን ዒላማ ማድረጓን አስታውቃለች።
📌 Kaynak
Bu haber XML kaynağından derlenmiştir. Tamamı için orijinal habere gidin.
Orijinal haberi oku →