ትራምፕ “የተኩስ አቁሙ አብቅቷል” ካሉ በኋላ ዛሬ ምሽት በድጋሚ በኢራን ላይ ከባድ ጥቃት እንደሚፈፅሙ ዛቱ
አሜሪካ በኢራን ውስጥ ጥቃቶችን ከፈጸመች እና ኢራን በአካባቢው ያሉ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች ላይ የአጸፋ እርምጃ መውሰዷን ካሳወቀች በኋላ በሁለቱ ወገኖች መካከል የነበረው የተኩስ አቁም ማብቃቱን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስታውቀዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አገራቸው ዛሬ ምሽት በኢራን ላይ በድጋሚ ከባድ ጥቃት እንደምትፈፅም ተናገሩ።
ትራምፕ ይህን ያሉት በኔቶ ጉባኤ ላይ ከዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ጋር በመሆን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው።
በመግለጫው ላይ ኢራንን በተመለከተ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ “ባለፈው ምሽት በከባዱ መትተናቸዋል፤ በጣም በጣም በከባዱ” ያሉ ሲሆን፣ አገራቸው ምናልባት ዛሬ ምሽት በድጋሚ ከባድ ጥቃት እንደምትፈፅም ተናግረዋል።
ትራምፕ ጨምረውም "ትንሽ ማስጠንቀቂያ ሰጥቻቸዋለሁ፤ ዛሬ ማታ በድጋሚ በከባዱ እንመታቸዋለን” ብለዋል።
በኢራን ደስተኛ እንዳልሆኑ የገለፁት ትራምፕ፣ ቴህራን የኒውክሌር መሣሪያ መታጠቅ እንደማይፈቀድላት አሜሪካ ያላትን አቋም ደግመው ገልጸዋል።
ትራምፕ “ሙሉ ጉዳዬ ስለአገዛዝ ለውጥ አይደለም” ሲሉም የአገሪቷን የኒውክሌር መርሃ ግብር ለማስቆም የሚያስችሉ ብዙ ለውጦች መምጣታቸውን አክለዋል።
“ኢራን ከዚህ በኋላ የመካከለኛው ምሥራቅ ኃያል አይደለችም” ሲሉም የኢራንን አስተዳደር አጣጥለዋል።
📌 Kaynak
Bu haber XML kaynağından derlenmiştir. Tamamı için orijinal habere gidin.
Orijinal haberi oku →