ብልጽግና ፓርቲ ዕጩ ባላቀረበበት ትግራይ ክልል ምርጫ ይካሄዳል?

📌 Diğer 📰 BBC Amharic 🕐 27.03.2026
ብልጽግና ፓርቲ ዕጩ ባላቀረበበት ትግራይ ክልል ምርጫ ይካሄዳል?

ብልጽግና ፓርቲ፤ ምርጫ የመካሄዱ ነገር አጠራጣሪ በሆነበት ትግራይ ክልል ለሚገኙ የፓርላማ እና የክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች አንድም ዕጩ አለማቅረቡን ቢቢቢ የተመለከተው የዕጩዎች ዝርዝር ያሳያል። ስድስት ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሁለት ቅንጅቶች በበኩላቸው 101 ዕጩዎችን አስመዝግበዋል።

ብልጽግና ፓርቲ፤ ምርጫ የመካሄዱ ነገር አጠራጣሪ በሆነበት ትግራይ ክልል ለሚገኙ የፓርላማ እና የክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች አንድም ዕጩ አለማቅረቡን ቢቢሲ የተመለከተው የዕጩዎች ዝርዝር ያሳያል። ስድስት ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሁለት ቅንጅቶች በበኩላቸው 101 ዕጩዎችን አስመዝግበዋል።

በትግራይ የቀረበው ጠቅላላ ዕጩዎች ቁጥር በክልሉ ካሉት የፓርላማ እና የክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች ብዛት ያነሰ ነው። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አከራካሪ ባላቸው ስፍራዎች ላይ ውሳኔ ከማሳለፉ በፊት ይፋ የተደረገ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ እንደሚያመለክተው፤ በትግራይ ክልል በድምሩ 182 መቀመጫዎች አሉ።

ከዚህ ውስጥ 152 ያህሉ የክልል ምክር ቤት እንደሆኑ፤ 38ቱ ደግሞ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የትግራይ ተወካዮች እንደሆኑ ተጠቅሷል።

ምርጫ ቦርድ ከአንድ ወር ገደማ በፊት የካቲት 23/2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፤ "በትግራይ እና አማራ ክልል መንግሥታት መካከል አከራካሪ ሆነው የቆዩት አምስት የምርጫ ክልሎች"፤ ከትግራይ "ውጪ ሆነው ለብቻቸው" ምርጫ እንዲደረግባቸው መወሰኑን አስታውቋል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት፤ "በቀጥታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት" ምርጫ እንዲደረግ የወሰነባቸው የምርጫ ክልሎች "ሑመራ፣ አዲ ረመፅ፣ ኮረም ኦፍላ፣ ጠለምት እና ራያ" ናቸው።

ቢቢሲ አማርኛ በተመለከተው የዕጩዎች ዝርዝር ውስጥ በእነዚህ የምርጫ ክልሎች ለመወዳደር የተመዘገቡ ተወካዮች አልተካተቱም።

በትግራይ ክልል ከፍተኛ የዕጩዎች ቁጥር ያስመዘገበው ከህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ተነጥለው በወጡ ፖለቲከኞች የተመሠረተው ዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ነው።

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ የሆኑትን የፓርቲው ሊቀ መንበር ጌታቸው ረዳን ለውድድር ያላቀረበው ስምረት፤ ሰባት ዕጩዎችን ያስመዘገበው ለፓርላማ ወንበሮች ነው።

የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ እና የፓርቲው የውጭ ግንኙነት ኃላፊው ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወትን ጨምሮ 30 ዕጩዎች ደግሞ ለክልሉ ምክር ቤት ለመወዳደር ቀርበዋል።

ትንሳኤ ሰብዓ እንደርታ ፓርቲ 24 ዕጩዎችን ለፓርላማ እና ለክልል ምክር ቤት በማስመዝገብ በሁለተኝነት ተቀምጧል። ነጻነት እና እኩልነት እንዲሁም ራያ ራዩማ ፓርቲዎች በዕጩ ብዛት ተከታይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) እና ትንሳኤ ሥርዓት ቃንጪ ሃቂ እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች ቅንጅት የሆኑት ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት እና ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረትም ዕጩዎቻቸውን አስመዝግበዋል።

በደም አፋሳሹ ጦርነት ምክንያት ስድስተኛው አጠቃላይ ምርጫ ያልተካሄደበት የትግራይ ክልል፤ ላለፉት አምስት ዓመታት በሕዝብ ተወካዮች እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት ውስጥ አልተወከለም። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ የተነሳ በአገር አቀፍ ደረጃ ምርጫ በተራዘመበት ወቅት ለብቻው ምርጫ በማካሄድ የመሰረተው የክልል ምክር ቤትም ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ ተበትኗል።

ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትግራይ ምርጫ እንደማይካሄድ በይፋ ባያሳውቅም፤ ከሌሎች አገሪቱ አካባቢዎች በተለየ በክልሉ የመራጮች ምዝገባ ሂደት አልተጀመረም።

በአገር አቀፍ ደረጃ የመራጮች ምዝገባ በተጀመረበት የካቲት 28/2018 ዓ.ም. ትግራይ ክልል ውስጥም ተመሳሳይ ሂደት ለማከናወን ዕቅድ የነበረ ቢሆንም "በተለያዩ ምክንያቶች ሳይሳካ" መቅረቱን የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ መናገራቸው አዲስ ማለዳ ተዘግቦ ነበር።

ሰብሳቢዋ የምርጫ ምዝገባ ሂደቱ ወደፊት እንደሚጀመር በወቅቱ እንደገለጹም ተነግሯል። እስካሁን ድረስ ግን በክልሉ የመራጮች ምዝገባ አለመጀመሩን ቢቢሲ ትግርኛ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ምርጫ ቦርድ፤ በክልሉ የሚገኙ ምርጫ ክልሎች እና የምርጫ ጣቢያ ጽሕፈት ቤቶች እንዲዘጋጁለት ከታኅሣሥ ጀምሮ ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ያቀረባቸው ጥያቄዎች እስካሁን ምላሽ አለማግኘታቸውን ምንጮች ተናግረዋል።

ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ምንጭ፤ "በትግራይ ያለው ሁኔታ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል አይደለም" የሚል ድምዳሜ ላይ መደረሱን ለቢቢሲ ትግርኛ አስረድተዋል። ይሁን እንጂ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህንን ድምዳሜውን ለምርጫ ቦርድ አለማሳወቁን ጠቅሰዋል።

በቅርቡ ለቦርዱ ምላሽ ሊሰጥ እንደሚችል የተናገሩት ምንጩ፤ "ምርጫ የሕዝቦች መብት ቢሆንም፣ አሁን በትግራይ ምርጫ የሚካሄድበት ዕድል የለም ማለት ይቻላል" ብለዋል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጥር ላይ ከቦርዱ በድጋሚ ደብዳቤ ከተጻፈለት በኋላ፤ በምርጫ ጉዳይ ላይ "የጋራ መግባባት እና አቋም ለመያዝ" በሚል በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ስብሰባ ጠርቶ ነበር።

በዚህ ስብሰባ "አብዛኛዎቹ

📌 Kaynak

Bu özet BBC Amharic kaynağından otomatik derlenmiştir. Tamamı için orijinal habere gidin.

Orijinal haberi oku →
← Tüm haberlere dön