ከፍተኛ ውዝግብ ስላስነሳው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ ማን ምን አለ?

📌 Diğer 📰 BBC Amharic 🕐 24.02.2026
ከፍተኛ ውዝግብ ስላስነሳው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ ማን ምን አለ?

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአማራ እና ትግራይ ክልሎች መካካል "አከራካሪ ሆነው የቆዩ" የተባሉትን አምስት የምርጫ ክልሎች በተመለከተ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ደርሶኛል ያለውን ውሳኔ ይፋ ካደረገ በኋላ የሁለቱ ክልሎች የፖለቲካ ተዋንያን በየፊናቸው መግለጫዎችን አውጥተዋል። በትግራይ በኩል ጊዜያዊ አስተዳደሩን ጨምሮ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ፤ በአማራ በኩል የሚገኙት ደግሞ ለውሳኔው ድጋፋቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአማራ እና ትግራይ ክልሎች መካካል "አከራካሪ ሆነው የቆዩ" የተባሉትን አምስት የምርጫ ክልሎች በተመለከተ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ደርሶኛል ያለውን ውሳኔ ይፋ ካደረገ በኋላ የሁለቱ ክልሎች የፖለቲካ ተዋንያን በየፊናቸው መግለጫዎችን አውጥተዋል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት)፣ ዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) እና ሌሎችም ፓርቲዎች ውሳኔውን በብርቱ ተቃውመውታል።

በአፋር ክልል እና በደቡባዊ የትግራይ አካባቢዎች እንደሚንቀሳቀስ የሚነገርለት እና ከትግራይ ኃይሎች በወጡ ወታደራዊ አዛዦች የሚመራው የትግራይ የሰላም ኃይልም በተመሳሳይ ተቃውሞውን አሰምቷል።

በአማራ ክልል በኩል ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና አካላት በበኩላቸው "አከራካሪ" ስለተባሉት አካባቢዎች የተላለፈውን ውሳኔ በበጎ ተመልክተውታል።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) እና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) በመግለጫቸው ይህንን አመልክተዋል።

በኮለኔል ደመቀ ዘውዱ የሚመራው በወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት እና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴም ለውሳኔው ድጋፉን ሰጥቷል።

ምርጫ ቦርድ በአማራ እና ትግራይ መካካል "አከራካሪ ሆነው የቆዩ" የተባሉትን አምስት የምርጫ ክልሎች "ከትግራይ ውጪ ሆነው" ድምጽ እንዲሰጥባቸው በፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ መተላለፉን ያስታወቀው ሰኞ የካቲት 16/2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ ነበር።

መግለጫው ላይ "አከራካሪ" ተብለው የተጠቀሱት "የሁመራ፣ የአዲረመፅ፣ የኮረም ኦፍላ፣ የጠለምት እና የራያ አላማጣ ምርጫ ክልሎች" ናቸው። በእነዚህ አካባቢዎች የተነሳው "የይገባኛል ጥያቄ እስከሚፈታ ድረስ"፤ "ከትግራይ ውጪ ሆነው ለብቻቸው በቀጥታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ" እንዲካሄድባቸው እንደተወሰነ ተገልጿል።

"የክልል ምክር ቤት ምርጫው በአካባቢዎቹ ላይ የተነሳው የይገባኛል ውዝግብ በሕገ መንግሥት ውሳኔ ሲፈታ አመቺ ሁኔታ ተመርጦ ወደፊት እንዲካሄድ" ፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ እንዳስተላለፈ ቦርዱ አስታውቋል።

የምክር ቤቱን ውሳኔ በመቃወም የመጀመሪያውን መግለጫ ያወጣው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ነው። በሌተናንት ጄነራል ታደሰ ወረደ የሚመራው ጊዜያዊ አስተዳደር ውሳኔውን "ሕገ መንግሥቱን እና የፕሪቶሪያን ስምምነት በግልጽ የሚቃረን" ሲል ገልጾታል።

"ይህ ውሳኔ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸውን የትግራይ ሕገ መንግሥታዊ ወሰኖች በቀጥታ አደጋ ላይ ይጥላል" ብሏል።

ውሳኔው የተላለፈው "የትግራይ ሕዝብ ውክልና እና ድምፅ በሌለበት" የፌዴሬሽን ምክር ቤት እንደሆነ የጠቀሰው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፤ እርምጃውን "በጽኑ" አውግዟል።

"ይህ እርምጃ ሊያስከትል የሚችለው ከባድና ሰፊ መዘዝ ከግምት ውስጥ በማስገባት፤ ይህ አደገኛ መንገድ በአስቸኳይ እንደገና እንዲጤን እና እንዲታረም እንጠይቃለን" ብሏል።

ህወሓትም በበኩሉ ባወጣው መግለጫ "የፕሪቶሪያውን ስምምነት በግልጽ የሚጥስ እና በትግራይ ሕዝብ ሕልውና ላይ አደገኛ አደጋ የሚደቅን ነው" ሲል ተቃውሟል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ "ወደ ቀያቸው መመለስ የነበረባቸውን ወገኖቻችንን ተስፋ የሚያጨልም" እንዲሁም "አሁንም በወራሪዎች ሥር ሆነው ግፍና ስቃይ እየደረሰባቸው ያሉ ወገኖቻችንን ሕይወት አደጋ ላይ የሚጥል የጄኖሳይድ አዋጅ ነው" ሲልም በጠንካራ ቃላት ተቃውሟል።

"ከዚህም ባለፈ በትግራይ እና በአማራ ሕዝቦች መካከል አዲስ ግጭት ለመፍጠር የታለመ ሴራ ነው" ሲል ከስሷል።

የፌደራል መንግሥት "ሕገ መንግሥታዊ ሉዓላዊ የትግራይ መሬትን ለወራሪዎች አሳልፎ ለመስጠት እየሠራ ነው" ሲል የወነጀለው ህወሓት፤ "የትግራይ ሉዓላዊ መሬት እና የሕዝብ ሕልውና ጉዳይ የማይታለፍ ቀይ መስመር" እንደሆነ በአጽንኦት አንስቷል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ተቃዋሚው ስምረት ውሳኔውን "ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት አልበኝትን የሚያውጅ" ሲል ጠርቶታል።

ፌዴሬሽን ምክር ቤት "ክልሎችን ከነባር አስተዳደራዊ መዋቅራቸው ውጪ በፌደራል መንግሥት ስር እንዲሆኑ የመወሰን ምንም ዓይነት ሕገ መንግሥታዊ ውክልና የለውም" ሲል የሕጋዊነት ጥያቄ አንስቷል።

በእነዚህ አካባቢዎች ላይ የተነሳው ውዝግብ መፈታት ያለበት በሕገ መንግሥቱ በተቀመጠው የክልሎች ወሰን አከላለል ለውጥ ድንጋጌ መሠረት እንደሆነ ጠቀሰው ስምረት፤ ይህ ሂደት አለመጠነቀቁን አስታውሷል።

"ይህ ሕጋዊ ሂደት ሳይጠናቀቅ እና በሕዝበ ውሳኔ ይፋዊ ለውጥ ሳይደረግ" ይህ ውሳኔ መተላለፉ "የክልል አስተዳደረን በጉልበት የመንጠቅ ሙከራ ነው" ብሏል። ውሳኔው በሕግ ፊት "ውድቅና የማይጸና" ነው የሚል አቋሙን ገልጿል።

ፌዴሬሽን ምክር ቤት

📌 Kaynak

Bu özet BBC Amharic kaynağından otomatik derlenmiştir. Tamamı için orijinal habere gidin.

Orijinal haberi oku →
← Tüm haberlere dön