"ሙስሊም ነኝ፤ እንዳትተኩሱብኝ": ከሆርሙዝ መዘጋት ቀጥሎ በሶማሊያ ያገረሸው የባሕር ላይ ውንብድና
በባሕረ ሰላጤው በኢራን ላይ ጦርነት ከተከፈተ በኋላ ዋነኛው የነዳጅ መተለላፊያ የሆርሙዝ ወሽመጥ በመዘጋሩ በኃይል አቅርቦት ላይ ቀውስ ተፈጥሯል። ይህንን ተከትሎ ደግሞ ጋብ ብሎ የነበረው የሶማሊያ የባሕር ላይ ወንበዴዎች በመርከቦች ላይ የሚፈጽሙት ዕገታ አገርሽቷል። ይህም በሌላኛው የባሕር መተላለፊያ ቀይ ባሕር መግቢያ ላይ እየተከሰተ ያለው የባሕር ላይ ውንብድና ከፍተኛ ስጋትን ፈጥሯል።
ባለፈው የሚያዝያ በአንዱ ዕለት የምሽት ጸሎት እንደተጠነቀቀቀ፤ ሳንቲ ሳናያ ስትፈራው የነበረውን መጥፎ ዜና ያረዳት መልዕክት ወደ ስልኳ ገባ።
የኢራን ጦርነት በተፋፋመት በዚያ ወቅት ባለቤቷ የሚመራው ነዳጅ ጫኝ መርከብ በመላው መካከለኛው ምሥራቅ ነዳጅ እያጓጓዘ ነበር።
መጋቢት 24/2018 ዓ.ም. ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የተነሳው ካፒቴን አሻሪ ሳማዲኩን በሆርሙዝ ወሽመጥ ዙሪያ የተፈጸሙ ጥቃቶችን ለጥቂት ቢያመልጥም፤ በመጨረሻ ግን የባሕር ላይ ወንበዴዎች ወደሚንቀሳቀሱበት ቀጣና ገባ።
የሁለት ልጆች አባት የሆነው የመርከቧ ካፒቴን በኢንዶኔዥያ ሱላዌሲ ደሴት የሚኖሩትን ቤተሰቦቹን በሚያነጋግርበት ወቅት ስጋት እንዳይገባቸው ለማድረግ ይጥር ነበር። የመንግሥትን ነዳጅ እንደጫነ በመግለጽ "እንደ ፈጣሪ ፈቃድ፤ ምንም አይፈጠርም" ይላቸው ነበር።
ሚያዝያ 13 ላይ ግን ""መርከቤ በባሕር ወንበዴዎች ጥቃት እየተፈጸመበት ነው" የሚል የድምጽ መልዕክት ወደ ባለቤቱ ላከ።
ከሶማሊያ ባሕር ዳርቻ አቅራቢያ ክላሽንኮቭ እና ሮኬት ማስወንጨፊያ የታጠቁ ወንበዴዎች ወደ ሞቃዲሾ እየቀዘፈች በነበረችው 'መርቸንት ታንከር ኦነር 25' የተባለች መርከብ ላይ የደፈጣ ጥቃት ፈጸሙ። የመርከቡን 17 ሠራተኞች እና ጭኖ የነበረውን 18,500 በርሜል ነዳጅ ያዙ።
ይህ የተሳካ ጠለፋ በአንድ ወቅት የአፍሪካ ቀንድን ስጋት ውስጥ ከትቶ የነበረው ከፍተኛ ገንዘብ የሚገኝበት እና በኃይል የተሞላው ውብድና ዳግም ማንሰራራቱን የሚጠቁም ክስተት ሆኗል።
ሳንቲ እንደምትናገረው የባሕር ላይ ወንበዴዎቹ ወደ መርከቡ መውጣት እስከሚጀምሩ ድረስ ባለቤቷ መርከቡን አላወቀም ነበር።
አሻሪ "እባካችሁ አትተኩሱብኝ፤ ሙስሊም ነኝ" ሲል አንድ የሚያደርጋቸውን እምነት ጠቅሶ ተማጸናቸው። "ከዚያ በኋላ የመርከቧ ሠራተኞች በአንድ ላይ እንዲሰበሰቡ ታዘዙ፣ ስልኮቻቸውም በሙሉ ተወሰዱ" ስትል ሳንቲ ትናግራለች።
ለዓመታት ጠፍቶ የነበረው በሶማሊያ የባሕር ዳርቻ የሚፈጸም የባሕር ላይ ዝርፊያ በኢራን ጦርነት በተፈጠረው ቀጣናዊ አለመረጋጋት ምክንያት በድጋሚ አገርሽቷል።
ታጣቂዎቹ 'ኦነር 25' በያዙ በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ ደግሞ ሲሚንቶ የጫነ 'መርቸንት ቬስል ስዋርድ' እንዲሁም የኤምሬቶች ንብረት የሆነውን ነዳጅ ጫኝ 'ዩሬካ' መርከቦችን አግተዋል።
ታጣቂዎቹ መርከቦቹን ከጠለፉም በኋላ በሶማሊያ የባሕር ወንበዴዎች መናኽሪያ ወደ ሆነችው ከፊል ራስ ገዟ የሰሜን ምሥራቅ ክልል ፑንትላንድ ወስደዋቸዋል።
ዓለም አቀፍ የባሕር ኃይል ጥበቃዎች ይህንን ዓይነቱን ስጋት ካስቆሙ አሥር ዓመታት ከሚበልጥ ጊዜ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ፤ የሶማሊያ የባሕር ላይ ወንበዴዎች እንደሆኑ የተጠረጠሩ ቡድኖች ሦስት የንግድ መርከቦችን እና ሠራተኞቻቸውን አግተዋል።
መርከቦቹ ላይ የነበሩት ባሕርተኞች ከግብፅ፣ ከሕንድ፣ ከኢንዶኔዥያ፣ ከፓኪስታን እና ከሶሪያ የመጡ ናቸው።
ቀጣናዊ ፀረ የባሕር ላይ ውንብድና ዘመቻዎችን የሚመራው የአውሮፓ ኅብረት የባሕር ኃይል "የባሕር ላይ ውንብድና ቡድኖች በሆርሙዝ ወሽመጥ ያለውን ቀውስ ሕገ ወጥ ተግባራቸውን ዳግም ለመጀመር እንደ አዲስ ምቹ አጋጣሚ ወስደውት ሊሆን ይችላል" ሲል ለቢቢሲ ገልጿል።
የሶማሊያ የባሕር ውንብድና መመለስ ለዓለም አቀፍ የመርከብ ጉዞ "እጅግ አስከፊ" እንደሚሆን በአቴንስ ፓንቴዮን ዩኒቨርሲቲ ረዳት ፕሮፌሰር እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዕፅ እና የወንጀል ጽሕፈት ቤት የዓለም አቀፍ የባሕር ትራንስፖርት ወንጀል ፕሮግራም አማካሪ የሆኑት ሶፊያ ጋላኒ ይናገራሉ።
"ሁቲዎች በቀይ ባሕር ከደቀኑት ስጋት እንዲሁም መርከቦች በሆርሙዝ ወሽመጥ እና በዙሪያው ከሚያጋጥማቸው አደጋ ጋር ሲዳመር፤ ከአረቢያን ባሕር እስከ አፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣና ለመንቀሳቀስ እጅግ አደገኛ ወደሆነ ካባቢ ሊቀይረው ይችላል" ሲሉ የስጋቱን መጠን አስረድተዋል።
"ይህም የኢንሹራንስ ክፍያዎችን እና የመርከብ ጉዞ ወጪዎችን ከፍ ስለሚያደርግ በመጨረሻም በምርቶች ዋጋ እና በሸማቾች ላይ ጫና ያሳድራል" ብለዋል።
ሠፊው የሶማሊያ የባሕር ዳርቻ እና የባሕር ውንብድና የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ የሆኑት በአውሮፓውያኑ 2000ዎቹ ውስጥ ነው።
በወቅቱ የውጭ አገር አሳ አጥማጆች በአገሬው ኅልውና ላይ ስጋት ደቅነው ነበር። ይህንን አጋጣሚ የተጠቀሙበት የወንጀል ቡድኖች ለሚያካሂዱት ጀልባዎችን የማገት እና ማስለቀቂያ የመቀበል ተግባር ከማኅበረሰቡ ድጋፍ ማግኘት ችለዋል።
የሚፈጸመው ጥቃት ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰው በአውሮፓውያኑ 2011 ነበር። በዚያ ዓመት ብቻ 237 ክስተቶች መመዝገባቸውን የዓለም አቀፉ የባሕር ትራንስፖርት ቢሮ መረጃ ያሳያል።
በጥር 2011 የሶማሊያ የባሕር ወንበዴዎች እስከ 32 የሚደርሱ መርከቦች
📌 Kaynak
Bu özet BBC Amharic kaynağından otomatik derlenmiştir. Tamamı için orijinal habere gidin.
Orijinal haberi oku →