በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የአሜሪካንን ባሕር ኃይል እየፈተኑ ያሉት የኢራን ትናንሽ ጀልባዎች
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የኢራንን ባሕር ኃይል እንዳወደሙ ቢናገሩም፣ ኢራን ትናንሽ ፈጣን ጀልባዎችን በመጠቀም በሆርሙዝ ወሽመጥ የመርከቦችን እንቅስቃሴን መግታት ችላለች። ስለእነዚህ ውጤታማ የኢራን ፈጣን ወታደራዊ ጀልባዎች ምን እናውያለን?
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ ባደረጉት ንግግር የኢራንን የባሕር ኃይል "ሙሉ በሙሉ አውድመናል" ብለዋል።
ከኢራን ባሕር ኃይል የቀረው "መትረየስ የተጠመደባቸው አነስተኛ ጀልባዎች" መሆናቸውን ተናግረዋል።
እነዚህ አነስተኛ የተባሉት ጀልባዎች በምዕራባውያን ተንታኞች ሞስኪቶ ፍሊት (mosquito fleet) የሚል ስያሜ ተሰጥቷቸዋል። በወባ ትንኝ የተመሰለው ስያሜያቸው መጠናቸውን እና ፍጥነታቸውን የሚያሳይ ነው።
ለወራት የኢራን መንግሥት በሆርሙዝ ወሽመጥ የመርከቦችን እንቅስቃሴ መግታት የቻለው በእነዚህ አነስተኛ ጀልባዎች ነው።
ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚደረግ እንቅስቃሴን በመግታት የዓለም ምጣኔ ሃብትን አናግታ አሜሪካ የምታደርስባትን ጥቃት እንድታቆም ጫና ማሳደር ትፈልጋለች።
አነስተኛ እና በፍጥነት ጥቃት የሚያደርሱ ጀልባዎች በኢራን መንግሥት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሠሩት በአውሮፓውያኑ በ1980ዎቹ በኢራን-ኢራቅ ጦርነት ወቅት ነው።
ኢራን እየተዋጋች የነበረው ከኢራቅ ጋር ቢሆንም ጦርነቱ ወደ ፋርስ ባሕረ ሰላሴ መስፋፋቱ አልቀረም። አሜሪካም ነዳጅ ጫኝ መርከቦችን ለመጠበቅ ስትል ወደ ጦርነቱ ገብታለች።
ከፍተኛ አቅም ያላቸው አገራትን ለመገዳደር በሚል አነስተኛ ጀልባዎች የጦርነቱ አካል እንዲሆኑም ተደረገ።
ኢራን ከሚሳዔል፣ ከሰው አልባ አውሮፕላን፣ ከባሕር ዳርቻ ከሚወነጨፉ መሣሪያዎች እና ፈንጂዎች በተጨማሪ እነዚህን አነስተኛ ጀልባዎች የውጊያ ስትራቴጂዋ አካል አድርጋለች።
በኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የሚመራው የትንንሽ ጀልባዎቹ ውጊያ ከተለመደው የባሕር ፍልሚያ የተለየ መንገድ ይከተላል።
የኢራን መንግሥትን የሚቃወመው ዩናይትድ አጌንስት ኒውክሌር ኢራን ከፍተኛ አማካሪ እና በቴነሲ ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑት ተባባሪ ፕሮፌሰር ሳይድ ጎላካር "የሚወሩት፣ የሚያደናግሩት፣ የሚያጠቁት እና የሚያሰናክሉት ጀልባዎች" በማለት ይገልጿቸዋል።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የአሜሪካን ባሕር ኃይል በተመለደው የውጊያ ስልት ማሸነፍ እንደማይችል እንደሚያውቅ ባለሙያው ይናገራሉ።
በፋርስ ባሕረ ሰላጤ የሚንቀሳቀሱ ኩባንያዎች ለአደጋ እንዲጋለጡ እና ወጪያቸው እንዲንር ማድረግ ዋነኛ አላማቸው ነው።
አነስተኛዎቹ ጀልባዎች በንግድ መርከቦች አቅራቢያ መተኮስን አንድ ስትራቴጂ አድርገው ይጠቀማሉ። ባሕር ላይ ፈንጂ ማጥመድ እና ከተለያዩ አቅጣጫዎች በርካታ ጀልባዎችን ማሰማራትም ሌላው ስልት እንደሆነ ተንታኞች ይገልጻሉ።
ፈጣን የሆኑት ጀልባዎች የጦር መሣሪያ፣ ሮኬት እና ፀረ መርከብ ሚሳዔል ይታጠቃሉ። አብዛኞቹ ጀልባዎች የሚመረቱት በኢራን ውስጥ ነው።
በዋሽንግተን የሚገኘው ሀድሰን ኢንስቲትዩት የባለሙያዎች ቡድን አባል ካን ካስፓጉሉ እንደሚሉት፤ ጀልባዎቹ በተመጣጣኝ ዋጋ የሚሸጡ እና በቀላሉ የሚተኩ ናቸው።
ኢራን እነዚህን ጀልባዎች በመጠቀም የንግድ እና ወታደራዊ መርከቦችን "በአነስተኛ ዋጋ" እንደምታስፈራራ ያስረዳሉ።
ኢራን የምትዝትባቸው መርከቦች ከፍተኛ ዋጋ የሚያወጡ ናቸው። ትንንሾቹ ጀልባዎች የባሕር ላይ ምጣኔ ሃብታዊ እንቅስቃሴን አደጋ ላይ ይጥላሉ።
እነዚህ ጀልባዎች ከውሃ በታች ዝቅ ብለው ይቆያሉ። በቅርብ እስከሚታዩ ድረስ መኖራቸውን ማወቅ ያዳግታል።
እነዚህ ጀልባዎች ትክክለኛ ቁጥራቸው አይታወቅም። ምክንያቱም አብዛኞቹ በኢራን ደቡባዊ የባሕር ዳርቻ በሚገኙ በዋሻ ውስጥ አልያም ከምድር በታች በተገነቡ ክፍሎች ተደብቀው እንዲቆዩ ይደረጋል።
ተንታኞች እንደሚሉት ከሆነ ኢራን ከ500 እስከ አንድ ሺህ የሚደርሱ ትንንሽ ጀልባዎች ሊኖሯት ይችላል።
የአሜሪካ ባሕር ኃይል የኢራን ጀልባዎች በዕይታ ውስጥ ከሆኑ መምታት የሚችልበት አቅም አለው። ስለዚህም እስላማዊ አብዮታዊ ዘቡ ጀልባዎችን ለመደበቅ ይሞክራል።
የሀድሰን ኢንስቲትዩት ባለሙያው ካን ካስፓጉሉ እንደሚሉት፤ እነዚህ ጀልባዎች ቀጥተኛ ውጊያ ውስጥ እንዲገቡ አይደረግም።
"የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ቀጥተኛ ውጊያ ላለማድረግ ይሞክራል። ጥቃት አድርሶ በፍጥነት መሸሽን እንደ ስልት ይጠቀማል። በተጨማሪም መውረር፣ ፈንጂ መጣል፣ በሰው አልባ አውሮፕላን መምታት፣ ሚሳዔል መጠቀም እና አነስተኛ ጀልባ ማሰማራት ይገኙበታል። አነስተኛ ጀልባዎች የአሜሪካ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ኪሳራ ያስከትላሉ" ይላሉ።
ኢራን ጀልባዎቹን በፍጥነት እና በአነስተኛ ወጪ ትተካለች። ከዚህ በተቃራኒው አሜሪካ እና አጋሮቿ የባሕር ላይ የንግድ እንቅስቃሴን ለማስቀጠል ውድ መርከቦችን ወይም አውሮፕላኖችን በማሰማራት ጥበቃ ማድረግ ግድ ይላቸዋል።
ኢራን መርከቦች ላይ ጥቃት ባትፈጽምም እንኳን መርከቦች ጥቃት ሊደርስባቸው ይችላል የሚለው ስጋት የኢንሹራንስ ዋጋ እንዲጨምር ያስገድዳል። ኩባንያዎች መርከባቸውን በዚያ መስመር እን
📌 Kaynak
Bu özet BBC Amharic kaynağından otomatik derlenmiştir. Tamamı için orijinal habere gidin.
Orijinal haberi oku →