መሪዎቹ እየተገደሉበት ባለበት ጸንቶ የቀጠለው የኢራን የጦርነት ወቅት አመራር የተዋቀረው እንዴት ነው?

📌 Diğer 📰 BBC Amharic 🕐 08.04.2026
መሪዎቹ እየተገደሉበት ባለበት ጸንቶ የቀጠለው የኢራን የጦርነት ወቅት አመራር የተዋቀረው እንዴት ነው?

ኢራን በአሜሪካ እና በእስራኤል እየተፈጸመባት ባለው ጥቃት ከጠቅላይ መሪዋ ከአያቶላህ አሊ ኻሜኒ ጀምሮ በርካታ ቁልፍ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ መሪዎቿ ተገድለውባታል። ነገር ግን አመራሯ ሳይፈረካከስ እየተተካካ ፍልሚያውን ቀጥሏል። ለመሆኑ የኢራን አመራር በዚህ ጦርነት ውስጥ ባለበት ጸንቶ እንዴት ሊቀጥል ቻለ?

በኢራን በኩል ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ጋር ድርድር እያደረጉ ያሉት የአገሪቱ ፓርላማ አፈ ጉባዔ መሐመድ ባጋር ጋሊባፍ መሆናቸው ሲገለጽ ቆይቷል።

ይህም ኢራን ጠቅላይ መሪዋ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ከተገደሉ በኋላ ማን እያስተዳደራት ነው? የሚል ጥያቄ አጭሯል።

ትራምፕ አምባገነን መንግሥታትን ለመገርሰስ ሲያስቡ በቬንዙዌላ ላይ የወሰዱት ዓይነት እርምጃን መተግበር ይሻሉ።

ሆኖም የኢራን ጠቅላይ መሪ መገደል የታሰበውን የሥርዓት ለውጥ አላመጣም። አገሪቱም የተዳከመች አትመስልም።

የኢራን እስላማዊ ዘብ እንዲህ ያሉ ጥቃቶችን መቋቋም በሚያስቸለው መንገድ እንደተዋቀረ ተንታኞች ይናገራሉ።

የኢራን አስተዳደር ወታደራዊ መዋቅሩን እንደያዘ ቀጥሏል። የኢራን የሥልጣን ክፍፍል በሃይማኖታዊ መሪዎች፣ በፖለቲከኞች እና በዋነኛነት በእስላማዊ አብዮቱ ዘብ ከፍተኛ አዛዦ ተከፋፍሏል።

የጦርነቱን መነሳት ተከትሎ ውሳኔ ሰጪው አካል የደኅንነት መዋቅሩ ሆኗል። ወታደራዊ ልምድ ያላቸው አመራሮችም በዚህ ይሳተፋሉ። የኢራን መደበኛ የአመራር ተዋረድ አሁንም ባለበት ይገኛል።

እስራኤል እና አሜሪካ በከፈቱት ጥምር ጥቃት የኢራን ከፍተኛ ባለሥልጣናት ቢገደሉም አስተዳደሩ በመንግሥት ሥራዎች እና በወታደራዊ ኃላፊነቶች ተከፍሎ ቀጥሏል።

አስተዳደሩ የተዋቀረው የከፍተኛ ባለሥልጣናት መገደል እንዳይንደው በተቀመረ አካሄድ እንደሆነ ተንታኞች ይገልጻሉ።

ከፍተኛ አመራሮች ሲገደሉ የሚተኳቸው ባለሥልጣናት መዘጋጀታቸውን የኢራን መገናኛ ብዙኃን ሲያስተጋቡ ይደመጣል። የቴህራን ባለሥልጣናትም ይህንኑ ደጋግመው ተናግረዋል።

ይህ የጠቅላይ መሪው ሥልጣን በእስላማዊ አብዮታዊ አመራር ውስጥ ከፍተኛው ነው። በወታደራዊ መዋቅር፣ በፍትሕ ሥርዓት እና በቁልፍ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ላይ ሥልጣን ይሰጣቸዋል።

በተግባር ግን አዲሱ ጠቅላይ መሪ ያላቸው ሥልጣንን በተመለከተ የጠራ መረጃ የለም። ከሕዝብ ዕይታ መራቃቸው እና አካላዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል የሚለው ጭምጭምታ ጥያቄዎች አስነስቷል።

አዲሱ ጠቅላይ መሪ ሥልጣን ከተረከቡ በኋላ እምብዛም በሕዝብ አልታዩም። በአስተዳደር እና ዲፕሎማሲ ረገድ ያላቸው የልምድ ማነስ በዚህ ፈታኝ ወቅት ዋነኛ አመራር እንዳይሆኑ ሊያግዳቸው ይችላል።

በአገሪቱ አስተዳደራዊ መርኅ መሠረት ከፍተኛው ሥልጣን የጠቅላይ መሪው ቢሆንም እንኳ፤ በዚህ የጦርነት ወቅት የዕለት ከዕለት ውሳኔዎች ላይ የሚደረሰው በከፍተኛ አመራሮች እና በአብዮታዊ ዘቡ ከፍተኛ አዛዦች ምክክር ይሆናል።

ስለዚህም አሁን ያለው የኢራን አስተዳደር ቅይጥ መልክ አለው። ማዕከሉን ያደረገው ጠቅላይ መሪውን ነው። ጠቅላይ መሪው የአንድነት ምልክት ተደርገው ይወሰዳሉ።

የኢራን እስላዊ አብዮታዊ ዘብ እና መደበኛ ሠራዊቱን ጥምረት የሚቆጣጠረው የማዕከላዊ ዕዝ ዋና ጽህፈት ቤት (ካህቱም አል-አንቢያ) በጦርነቱ ማዕከላዊ ቦታ የያዘውም ለዚህ ይሆናል።

በአውሮፓውያኑ 1979 የአብዮቱን ዕሳቤ እና አመራር ለማስጠበቅ የተቋቋመው አብዮታዊ ዘቡ ወደ ኃያል ወታደራዊ፣ ምጣኔ ሃብታዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር ተሻግሯል።

የኢራንን የባለስቲክ ሚሳዔል እንዲሁም የውጭ ዘመቻዎችን እና የአገር ውስጥ የደኅንነት እንቅስቃሴዎችን ይመራል።

የአያቶላህ አሊ ኻሜኒን ግድያን ተከትሎ የሥልጣን ሽግግርን ጨምሮ የቴህራንን አስተዳደራዊ መዋቅር እያስቀጠለ ያለው እስላማዊ አብዮታዊ ዕዝ ነው።

በአዲሱ ጠቅላይ መሪ ሹመት ውስጥም ቁልፍ ሚና እንዳለው ተንታኞች ይገልጻሉ። ከዚህ ቀደም በነበረው አሠራር መሠረት የኢራን ጠቅላይ መሪ ይፋዊ የመንግሥት ሥልጣን ባይኖራቸውም ከአብዮታዊ ዘቡ ጋር የቅርብ ትስስር አላቸው።

በተለይም ከጦርነቱ እና ቀጣናዊ ፖሊሲ ጋር የተያያዙ ስትራቴጂያዊ ውሳኔዎች ላይ የሚደረሰው በአብዮታዊ ዘቡ አማካኝነት ነው።

የእስላማዊ አብዮታዊ ዘቡ የቀድሞ እና የአሁንም አዛዦች በመላው አገሪቱ በምክር ቤት፣ በደኅንነት መዋቅሮች እና በቀጣናዊ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ ናቸው።

ይህ የሚከወነው በአንድ ሰው ሳይሆን በከፍተኛ ባለሥልጣናት እና ደጋፊዎቻቸው በሆኑ ፖለቲከኞች መዋቅር ውስጥ ነው። የኢራን አፈ ጉባዔ መሐመድ ባጋር ጋሊባፍ የዚህ መዋቅር አንድ አካል ናቸው።

የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ እያደረገ ያለው ተጽዕኖ ፈጣሪነት ከመዋቅሩ አሠራር ጋር የሚያያዝ ነው።

የአገሪቱ ከፍተኛ አመራሮች እየተገደሉ እና የጥቃት ዒላማ እየሆኑም አስተዳደሩ መቀጠል በሚችልበት መንገድ ነው የተዋቀረው።

በዚህ መዋቅር ውስጥ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ማዕከላዊ ሚናውን ይዞ ከመጋረጃ ጀርባ ዋነኛ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል።

የኢራን አፈ ጉባዔ መሐመድ ባጋር ጋሊባፍ በቴህራን በሕይወት ከሚገኙ ዋነኛ የፖለቲካ መዋቅሩ አባላት መካከል አን

📌 Kaynak

Bu özet BBC Amharic kaynağından otomatik derlenmiştir. Tamamı için orijinal habere gidin.

Orijinal haberi oku →
← Tüm haberlere dön