የሚሳዔል ዒላማ የሆኑት ቅንጡ ከተሞች፡ የኢራን ጦርነት በባሕረ ሰላጤው አገራት ውስጥ ምን ለውጥ ያስከትላል?
የቅንጦት እና የንግድ መናኸሪያዎች ሆነው የቆዩት የባሕረ ሰላጤው አገራት ቅንጡ ከተሞች በኢራን ላይ የተከፈተውን ጦርነት ተከትሎ ገጽታቸው እየተቀየረ ነው። አገራቱ በጦርነቱ ዳር ላይ የቆሙ ቢሆንም በየዕለቱ የኢራን ሚሳዔሎች እየጎበኟቸው ነው። ይህ ጦርነት በወደፊት ገጽታቸው ላይ ምን ውጤት ይኖረዋል?
የባሕረ ሰላጤው አገራት ለረዥም ጊዜ የመረጋጋት እና የቅንጦት ስፍራዎች ተደርገው ነበር የሚታዩት።
ሳዑዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ኩዌት፣ ኳታር፣ ኦማን እና ባህሬን ባለሀብቶችን፣ ዋና ዋና ኮርፖሬሽኖችን እና ክህሎት ያላቸውን ሠራተኞችን በመሳብ ረገድ ወደር አልነበራቸውም።
አውሮፕላን ማረፊያዎቻቸው ወደ ዓለም አቀፍ ማዕከላት፣ ከተሞቻቸው ደግሞ ወደ የፋይናንስ እና የቱሪዝም ማዕከላትነት ተለውጠዋል።
ነገር ግን አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱት ጦርነት እና የኢራን አጸፋ ይህንን ምሥል አጠልሽቶታል።
ምክንያቱም በባሕረ ሰላጤው በሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ማዕከላትን ዒላማ ያደረጉ የኢራን ሚሳዔሎች እና ድሮኖች በሲቪል እና በኢነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል።
ለምሳሌ የኳታር መንግሥት ከቤት መሥራትን ወዲያውኑ አስቁሞ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተቋረጠው ትምህርት ዳግም እንዲጀመር አድርጓል።
ነገር ግን አንዳንድ ባለሙያዎች የባሕረ ሰላጤው አገራት ይህንን አስከፊ ሁኔታን መቋቋም ቢችሉም፣ ጦርነቱ ግን አንዳንድ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮችን መለስ ብለው እንዲቃኙ አስገድዷል ብለው ይከራከራሉ።
"ከኢራን የሚሰነዘረውን ጥቃት ማስቆም አይቻልም፤ ምክንያቱም ከመልክዓ ምድር አንጻር ያለ ቅርበት ነው" ይላሉ በዋሽንግተን የሚገኘው የመካከለኛው ምሥራቅ ኢንስቲትዩት ባልደረባ አሌክስ ቫታንካ።
"እነዚህ አገራት አሁን ቅርቃር ውስጥ ገብተዋል፤ የእነርሱ ባልሆነ ጦርነት ከፊት የተሰለፉ መንግሥታት ሆነዋል፤ ለዚያም ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዋጋ እየከፈሉ ነው።"
አክለውም "ገንዘባቸውን በሙሉ ለመከላከያ ቢያውሉም፣ ያየነው እነዚህ አገራት ለኢራን በጣም ቀላል ዒላማዎች መሆናቸው ነው፤ የቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንታቸው ጥቂት ሺህ ዶላር ዋጋ ባላቸው የኢራን ድሮኖች አደጋ ላይ ወድቋል" ብለዋል።
ይህ አለመመጣጠን የኢንሹራንስ ወጪን ያንራል፤ የሎጂስቲክስ ጉዳዮችን ያወሳስበዋል፤ እንዲሁም ኩባንያዎች ለባሕረ ሰላጤው ያላቸውን ተጋላጭነት እንደገና እንዲያስቡ ሊያደርጋቸው እንደሚችል ቫታንካ ተናግረዋል።
የባሕረ ሰላጤው አገራት በአሜሪካ እና በኢራን መካከል አስቸጋሪ የሆነ መስመር ሲጓዙ፣ አንዱ አሁናዊ አደጋ ከዋሽንግተን ጋር የደኅንነት ትብብራቸውን ማደስ ነው ሲሉ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሚገኘው የኤምሬትስ ፖሊሲ ማዕከል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኤብተሳም አል ኬትቢ ይከራከራሉ።
የባሕረ ሰላጤው አገራት "አሁን በተፈጠሩት የደኅንነት ስጋቶች ምክንያት ያለ ምንም ኮሽታ ወደ አሜሪካ እና ወደ እስራኤል እየተጠጉ ነው" ይላሉ።
ነገር ግን ይህ ትብብር ተግባራዊ እንጂ የርዕዮተ ዓለም እንዳልሆነ አጽንዖት ሰጥተዋል። "ወደ ጦርነቱ ዘልቀው እንዳይገቡ፣ ዋና ዒላማዎች እንዳይሆኑ እንዲሁም ስትራቴጂካዊ ነፃነት እንዳያጡ ይጠነቀቃሉ።"
ቫታንካ በተለይም የአሜሪካን ባሕረ ሰላጤ ለመከላከል ፈቃደኛነት በተመለከተ የጠበቀ የደኅንነት ትስስር ገደብ እንዲኖረው ያስጠነቅቃሉ።
የባሕረ ሰላጤው መንግሥታት ከግጭቱ በፊት ዋሽንግተንን ስለ ጦርነቱ ያላቸውን ስጋት ከረጅም ጊዜ በፊት አስጠንቅቀው እንደነበር እና በዚህም ደስተኛ አለመሆናቸውን ተናግረዋል።
"ትራምፕ ለኔታንያሁ ሲሉ ወደ ጦርነት ሲገቡ የባሕረ ሰላጤውን አገራት ችላ ብለዋል" የሚሉት ባለሙያው "እንደ እስራኤል ሊታዩ እንደማይችሉ ያውቃሉ" ሲሉ ያስረዳሉ።
የአሜሪካ የውስጥ ፖለቲካ ዋሽንግተን የባሕረ ሰላጤ አገራትን ለመከላከል ምን ያህል ርቀት እንደምትሄድ እንደሚገድብም በመጥቀስ ይሞግታሉ።
"የአሜሪካ ሕዝብ በባሕረ ሰላጤው ቀጣና ውስጥ ባሉ የጦር ሰፈሮች ላይ የሚደርስ ጥቃትን በቸልታ ማየት ይፈልጋል?...እንዴት ነው ይህ የሚታየው? ይህ አሜሪካን ታላቅ ከማድረግ እንቅስቃሴ በተቃራኒው የቆመ ነው። [ፕሬዚዳንት ትራምፕ] አሜሪካ በውጭ አገራት ጦርነት የምታደርገው ጣልቃ ገብነት አገሪቱን ያዳክማል የሚል ሃሳብ ነበር የሚያቀነቅኑት።"
ኢራን በበኩሏ የባሕረ ሰላጤ አገራት በጦርነቱ ውስጥ ገለልተኛነት እንዲሆኑ ጫና እያሳደረች ነው ሲሉ ቫታንካ ይናገራሉ።
"የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከባሕረ ሰላጤው አገራት መካከል አንዳቸውም አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱትን ጦርነት አላወገዙም ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል…ኢራን 'ከዚህ ውጊያ ራሳችሁን አስወጡ' እያለቻቸው ነው።"
የባሕረ ሰላጤው መንግሥታት "በኢራን ላይ በጣም ተቆጥተዋል" ቢሉም ዋና ዒላማ ከመሆን መቆጠብ እንደሚፈልጉም አልሸሸጉም።
ስልታቸው በአሜሪካ ወይም በእስራኤል እርምጃዎች ላይ በግልጽ ሳይሳተፉ ራሳቸውን መከላከል እንደሆነ ተናግረዋል።
"ኢራን ሰዎች በእነዚህ አገሮች ውስጥ መኖርን አስቸጋሪ እንዲሆንባቸው እያደረገች ነው። ይህም ለትውልድ የሚቀጥል የኅልውና አደጋ ሊ
📌 Kaynak
Bu özet BBC Amharic kaynağından otomatik derlenmiştir. Tamamı için orijinal habere gidin.
Orijinal haberi oku →