የኢራን ሚሳዔሎች ወደ ታላላቆቹ የአውሮፓ ከተሞች ሊደርሱ ይችላሉ?
ኢራን በሕንድ ውቅያኖስ ዲያጎ ጋርሲያ ደሴት ላይ ወደሚገኘው የዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) እና የአሜሪካ የጋራ ወታደራዊ ሰፈር ላይ የረዥም ርቀት ባለስቲክ ሚሳዔሎችን ማስወንጨፏ በመካከለኛው ምሥራቅ ያለውን ግጭት እየተባባሰ መምጣቱን ያሳያል። በእርግጥ ሚሳዔሎቹ ወደታቀደላቸው ዒላማ ሳይደርሱ ቀርተዋል። ነገር ግን የእስራኤል የመከላከያ ሠራዊት ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ እንዲህ ዓይነት የረዥም ርቀት ሚሳዔሎች ጥቅም ላይ ሲውሉ ይህ የመጀመሪያው እንደሆነ ተናግሯል።
ኢራን በሕንድ ውቅያኖስ ዲያጎ ጋርሲያ ደሴት ላይ ወደሚገኘው የዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) እና የአሜሪካ የጋራ ወታደራዊ ሰፈር ላይ የረዥም ርቀት ባለስቲክ ሚሳዔሎችን ማስወንጨፏ በመካከለኛው ምሥራቅ ያለውን ግጭት እየተባባሰ መምጣቱን ያሳያል።
በእርግጥ ሚሳዔሎቹ ወደታቀደላቸው ዒላማ ሳይደርሱ ቀርተዋል። ነገር ግን የእስራኤል የመከላከያ ሠራዊት ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ እንዲህ ዓይነት የረዥም ርቀት ሚሳዔሎች ጥቅም ላይ ሲውሉ ይህ የመጀመሪያው እንደሆነ ተናግሯል።
ቴህራን እስካሁን ድረስ ሚሳዔሎቹን መተኮሷን በይፋ አላረጋገጠችም፤ የኢራን ሚዲያዎችም ቢሆኑ በዘገባዎቻቸው በአብዛኛው የውጭ መገናኛ ብዙኃንን ብቻ ጠቅሰዋል።
ባለሙያዎች አሁን የከሸፈው ጥቃት እንዲሁም በርቀት ለሚገኙ ዒላማዎች ይህ ምን ማለት እንደሆነ ጨምሮ የራሳቸውን ትንታኔ እየሰጡ ነው።
በርሊን፣ ፓሪስ እና ለንደንን ጨምሮ የአውሮፓ ዋና ዋና ከተሞች በቴህራን ሚሳዔሎች ዒላማ ሊሆኑ ይችላሉ?
የዩኬ የካቢኔ ሚኒስትር የእስራኤሉ መከላከያ እንደሚለው ኢራን ለንደን መድረስ የሚችሉ የረዥም ርቀት ሚሳዔሎች እንዳሏት "ለማረጋገጥ የሚያስችል ምንም ዓይነት ግምገማ የለም" ብለዋል።
የቢቢሲ ኒውስ ፐርሺያ ባልደረባ ጎህኔህ ሃቢቢያዛድ "የኢራን የሚሳዔል ፕሮግራም ለረዥም ጊዜ የዓለም አቀፍ ትኩረት ማዕከል ሆኖ ቆይቷል" ይላል።
"ቴህራን የሚሳዔል ግንባታዋ ሙሉ በሙሉ ለመከላከል እና በብሔራዊ የመከላከያ ስትራቴጂ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ብትናገርም፣ ተቺዎች ግን ረዥም ርቀት የመምዘግዘግ አቅም ያላቸው መሣሪያዎች የአካባቢውን የደኅንነት ሁኔታ ሊለውጥ እንደሚችል ይከራከራሉ።"
እስራኤል እና አሜሪካ በጋራ ኢራን ላይ ጥቃት ሲከፍቱ በቴህራን የኒውክሌር መረሃ ግብር ላይ ያሉ ስጋቶችን ለመፍታት ድርድር እየተደረገ ነበር።
የዲያጎ ጋርሲያ አካል የሆነባቸው የቻጎስ ደሴቶች ከኢራን በግምት 3,800 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛሉ።
ዎል ስትሪት ጆርናል እና ሲኤንኤን ስማቸውን ያልጠቀሷቸውን የአሜሪካ ባለሥልጣናትን መሠረት አድርገው ሁለት የባለስቲክ ሚሳዔሎች ወደ ደሴቱ መተኮሳቸውን ዘግበዋል።
አንደኛው ሚሳኤል በአየር ላይ እየተምዘገዘገ ሳለ መውደቁ ሲገልጽ፣ ሌላኛው ደግሞ በአሜሪካ የጦር መርከብ መክሸፉ ተነግሯል። ቢቢሲ ዘገባዎቹ ትክክለኛ መሆናቸውን ተረድቷል።
ኢራን ወደ ደሴቲቱ ሚሳዔሎችን ካስወነጨፈች በኋላ ብዙም ሳይቆይ የእስራኤል ጦር አባል በአውሮፓ፣ በእስያ እና በአፍሪካ በርካታ ከተሞች አሁን ለአደጋ የተጋለጡ መሆናቸውን እና ባለፈው ዓመት ቴህራን እንዲህ ዓይነት አቅም ያላቸውን ሚሳዔሎች ለማምረት እንዳሰበች መሳወቃቸውን ተናግረዋል።
የእስራኤል ጦር ዋና አዛዥ ሌተናንት ጄኔራል ኢያል ዛሚር ወደ ቻጎስ ደሴቶች ሚሳዔል ከተተኮሰ በኋላ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ባስቀመጡት የቪዲዮ መልዕክት ግልጽ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
"ኢራን 4,000 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ወደሚገኝ ዒላማ ሁለት አህጉር አቋራጭ ባላስቲክ ሚሳዔሎችን አስወንጭፋለች። ሚሳዔሎቹ እስራኤልን ለመምታት የታሰቡ አልነበሩም" ብለዋል። "ሚሳዔሎቹ የሚሸፍኑት ርቀት እስከ የአውሮፓ ዋና ከተሞች ይደርሳል። በርሊን፣ ፓሪስ እና ሮም ሁሉም በቀጥታ ለአደጋ የተጋለጡ ናቸው።"
የቀድሞው የዩኬ ጥምር ጦር አዛዥ ጄኔራል ሰር ሪቻርድ ባሮንን ጨምሮ ሌሎች የመከላከያ ባለሙያዎች፤ ይህ ሁሉ የኢራንን የሚሳዔል ክምችት እና ተደራሽነት እንደገና መገምገም እንዳስገደዳቸው ለቢቢሲ ተናግረዋል።
"ቀደም ሲል የኢራን ሚሳዔሎች 2,000 ኪ.ሜ ርቀት መወንጨፍ እንደሚችሉ እናስብ ነበር፤ ዲያጎ ጋርሲያ ደግሞ 3,800 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች።"
ኢራን እስካሁን ድረስ በባላስቲክ ሚሳኤል ፕሮግራሟ ላይ ራሷ ላይ ገደብ ማስቀመጧን በመግለጽ ወደ 2,000 ኪ.ሜ የሚወነጨፉ ብቻ እንዳላት ተናግራለች። ይህ ማለት እስራኤል በኢራን ሚሳዔሎች ርቀት ውስጥ ስትሆን የአውሮፓ አገራት ግን አይደሉም።
ሟቹ የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ በ2021 ምንም እንኳ ወታደራዊ መሪዎች እና አብዮታዊ ዘቡ ባይስማማም ይህ ውሳኔ የፖለቲካ ምርጫ እንጂ ሚሳዔሎችን በማምረት ረገድ የአቅም ገደቦች ኖረው አለመሆኑን ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ባለፈው ዓመት መስከረም ወር ላይ አንድ የኢራን የፓርላማ አባል ለመንግሥት ቴሌቪዥን እንደተናገሩት፤ አብዮታዊ ዘቡ አህጉር አቋራጭ የባለስቲክ ሚሳዔል በተሳካ ሁኔታ መሞከሩን ጠቅሰው ሚሳዔሉ ስለሚሸፍነው ርቀት ግን ሳይገልጹ ቀርተዋል።
በተጨማሪም የአሜሪካ ባለሥልጣናት የኢራን የጠፈር ፕሮግራም አህጉር አቋራጭ የባለስቲክ ሚሳዔሎችን እንድትገነባ የሚያስችሏትን ቴክኖሎጂዎችን እንዳዘጋጀ ለረጅም ጊዜ ሲናገሩ ቆይተዋል።
በለንደን የሚገኘው የሮያል ዩናይትድ ሰርቪስ ኢንስቲትዩት የቀድሞ
📌 Kaynak
Bu özet BBC Amharic kaynağından otomatik derlenmiştir. Tamamı için orijinal habere gidin.
Orijinal haberi oku →