'ወራጅ አለ'፡ የአሜሪካዊቷ ሙዚቀኛ የኢትዮጵያ ትዝታዎች
የኢትዮጵያን ሙዚቃ ማጣጣም ከጀመረች ከ20 ዓመታት በላይ አስቆጥራለች። አዲስ አበባ ደግሞ 11 ዓመታት ኖራለች። ኬታ ሆስታተር ትባላለች። ቫዮሊን ተጫዋች እንዲሁም ሙዚቃ አቀናባሪ ናት። ከሰሞኑ ‘ወራጅ አለ’ የተሰኘውን የመጀመሪያ አልበሟን ለቅቃለች። ስለ አዲሱ አልበሟ፣ ስለ አዲስ አበባ ቆይታዋ እና ስለ ኢትዮጵያ ሙዚቃ ከቢቢሲ ጋር ቆይታ አድርጋለች።
የኢትዮጵያን ሙዚቃ ማጣጣም ከጀመረች ከ20 ዓመታት በላይ አስቆጥራለች። አዲስ አበባ ደግሞ 11 ዓመታት ኖራለች።
ከሰሞኑ 'ወራጅ አለ' የተሰኘውን የመጀመሪያ አልበሟን ለቅቃለች። ለእሷነቷ ቅርብ የሆነ፣ ለዓመታት ስትማር የቆየቻቸው ነገሮች መገለጫ እና ታላቅ የጥበብ ሥራዋ እንደሆነ ትገልጻለች።
የአልበሙ የመጀመሪያ ሙዚቃ 'ሙዚቃዊ ስሌት' ነው። አስከትሎም ትዝታ፣ ልበይ፣ ሬጌ ከሚሴ፣ ጎንደር፣ ወይዘሪት ኢትዮጵያ እና በሎሚ በና ይደመጣሉ።
አብዛኞቹ ሙዚቃዎች የኢትዮጵያ ሙዚቃ "ወርቃማ ዘመን" ተብሎ ከሚሞካሸው ወቅት የተወሰዱ ናቸው። ሙዚቃዎቹ የቀደመ ግርማ ሞገሳቸው እንዳለ ሆኖ፣ በቫዮሊን ተከሽነው አድማጭ ጆሮ ይደርሳሉ።
'ወራጅ አለ' አልበም ውስጥ የተካተቱት የኢትዮጵያ ሙዚቃዎች የቫዮሊን ብቻ ሳይሆን ኤሌክትሮኒክ ድምጽም አላቸው። እያንዳንዳቸው የየራሳቸውን ታሪክ የሚናገሩ ይመስላሉ።
ሙዚቃዎቹን "ኢትዮጵያ ቤቴ ሳለች ባሳለፍኳቸው ዓመታት የነበረው ድባብ፣ የሰዎች ምሥሎች እና የአላፊ ቅጽበቶች ስብስብ" ስትል ትገልጻቸዋለች።
"የዚህ አልበም መለቀቅ በጣም አስደሳች ስሜት የሚሰጥ ነው" ትላለች ኬታ። "የደስታ ጣሪያ" ብላ የምትገልጸውን ስሜት እንዳላበሳት ትገልጻለች።
ሙዚቃዎቹን የኢትዮጵያ ቆይታዋ አካል ለማለት ይቻላል። በእሷ አገላለጽ "ማለት የምትፈልገውን ያስተላለፈችባቸው" ናቸው።
እሷ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ ያላትን ሚና እንዲሁም ኢትዮጵያውያን አርቲስቶች ያበረከቱላትን አስተዋጽኦ የገለጸችበት አልበም መሆኑን ትናገራለች።
አልበሙን ከእሷ ጋር መነጋገር እንደሚቻልበት መንገድ ትወስደዋለች። ለዚህም ነው "ለሰዎች ኢትዮጵያ ስላለው ሕይወቴ ከምነግራቸው ይልቅ አልበሙን ገዝተው ታሪኬን ይሰማሉ" የምትለው።
ወደ ኢትዮጵያ ከመሄዷ በፊት ስላለው ሕይወቷ እና ኢትዮጵያ ከኖረች በኋላ ምን ዓይነት ሰው እንደሆነች በጥበብ ዐይን ማሳየት መቻሏ ያስደስታታል።
የውጭ ዜጎች ኢትዮጵያን ሲረግጡ ከሚማሯቸው የመጀመሪያዎቹ ቃላት ወይም አገላለጾች አንዱ መሆኑ ለኬታ ትርጉም አለው።
የአዲስ አበባን ታክሲዎች ያለ 'ወራጅ አለ' ማሰብ ይከብዳል። በተለይ ደግሞ ቋንቋውን የማይችል ሰው 'ወራጅ አለ'ን አጥብቆ ከመያዝ ውጭ አማራጭ አይኖረውም።
ኬታ እንደማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ መጀመሪያ የተማረችው ሐረግ 'ወራጅ አለ' እንደነበር ታስታውሳለች።
". . .ሚኒባሱ ውስጥ አብረን ነን። እዚያ ጋር ወራጅ አለ። ከዚያ ደግሞ ወደዚህ ቦታ ልውሰዳችሁ። በሙዚቃዬ ሥዕሉን ልሣልላችሁ። ከዚያ ወራጅ አለ። በድጋሚ ሚኒባሱን ተሳፍረን ደግሞ ወራጅ አለ። ከዚያ ደግሞ ወደ ቀጣዩ ቦታ ልወስዳችሁ ነው. . ."
"ትዝታ፣ ቦታ እና ጊዜ ተደባልቀው ድርብርብ የቫዮሊን ሥነ ሕንጻ ሠርተዋል" ስትል ትገልጸዋለች።
በአንድ በኩል ከቦታ ቦታ ለመንቀሳቀስ ረድቷታል። በሌላ በኩል ደግሞ የተለያዩ ትንንሽ ታሪኮችን የያዘ አድርጋ ትወስደዋለች።
'ወራጅ አለ' የሚባለው ታክሲ ውስጥ ይሁን እንጂ የአዲስ አበባን ኑሮ፣ የኢትዮጵያን ኑሮ እና መጓጓዣን የሚያንጸባርቅ እንደሆነ ትናገራለች።
"መድረስ የሚፈልጉበት ቦታ ለመድረስ 'ወራጅ አለ'ን ማወቅ ግድ ነው። በውስጡም ማጋራት የምፈልጋቸውን ትንንሽ ታሪኮች ይዟል።"
በአልበሟ የኢትዮጵያ "ወርቃማ ዘመን" ሙዚቃዎችን ለማካተት የመረጠችው አንድም በብዙኃኑ ዘንድ ተወዳጅ ስለሆኑ ነው።
"ለመጀመሪያው የኢትዮጵያ አልበሜ እነዚህን ሙዚቃዎች የመረጥኩት ሆነ ብዬ ነው። የኢትዮጵያን ሙዚቃ የሰሙ ሰዎች የዚህ ታሪክ አካል እንደሆኑ እንዲሰማቸው በሚል ነው።"
ብዙዎች እነዚህን ሙዚቃዎች ያውቋቸዋል፤ አንዳች ትስስርም አላቸው። እነዚህ ለብዙዎች ስሜት ቅርብ የሆኑ ጥንታዊ ሙዚቃዎች በኬታ ዘመነኛ "ቫዮሊናዊ ዕይታ" ቀርበዋል ልንል እንችላለን።
አድማጮቿ ይሄንን ሙዚቃ አውቀዋለሁ ብለው መስማት ከጀመሩ በኋላ ረቂቅ ከሆነው የአልበሙ ቅንብር ጋር ታስተዋውቃቸዋለች።
ሙዚቃዎቿ በጣም ረቂቅ እና ሩቅ እንዳይሆኑ "የቅርብ መስኮት" የከፈተችበት መንገድ እንደሆነ ትናገራለች።
የድምጻውያኑ ቅላጼ፣ የሙዚቃ መሣሪያዎቹ፣ የሙዚቀኞቹ ክህሎት "በጣም የተለየ" እንደሆነ ታምናለች። "ግሩም እና ማራኪ ምት" ያለው ሙዚቃም ትለዋለች።
እንደ ቫዮሊን ተጫዋች እና ሙዚቃ አቀናባሪ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ስትገልጽ "የተነባበረ፣ አንዱ ከአንዱ የተሰናሰለ ምት ያለው" ብላ ነው። ወደ ቫዮሊኗ የምትወስደውም ይሄንን እንደሆነ ታስረዳለች።
የኢትዮጵያን ሙዚቃ ስትገልጽ ድባቡን፣ እንግዳ ተቀባይነቱን፣ ልኅቀቱን እና ለሙከራ የተመቸ መሆኑን ሳታነሳ አታልፍም።
ምናልባት የውጭ አገር ሰዎች መጀመሪያ ላይ ላይረዱት ቢችሉም ስለ ቅኝቶቹ ቁልፍ ነገሮችን ካወቁ በኋላ እንደሚዋሀዳቸው ትናገራለች።
ቫዮሊንን ከሌሎች የሙዚቃ መሣሪ
📌 Kaynak
Bu özet BBC Amharic kaynağından otomatik derlenmiştir. Tamamı için orijinal habere gidin.
Orijinal haberi oku →