'የማያመልጡት ወጥመድ'፡ እናት በመሆናቸው የሚጸጸቱት ሴቶች

📌 Diğer 📰 BBC Amharic 🕐 15.05.2026
'የማያመልጡት ወጥመድ'፡ እናት በመሆናቸው የሚጸጸቱት ሴቶች

. . . "እናትነት ባንፈልገው እንኳ የሚከተለን እና የምናከናውነው ማለቂያ የሌለው ሥራ ነው፣ ምክንያቱም ልጆቻችን በእኛ ላይ ጥገኛ ናቸው… የማናመልጠው ወጥመድ ይመስላል" ትላለች። እናት መሆን ምን ያህል "አስከፊ" እንደሆነም ያለማመንታት ትናገራለች። ስለልጇ ስትጠየቅ ግን ድምጸቷ ጭምር ብሩህ ይሆናል።

ካርመን የአስር ዓመት ልጇ ቲዮን በጣም ትወደዋለች። ወደኋላ ተመልሰሽ አንድ ነገር መቀየር ትችያለሽ ብትባል ግን እናት አልሆንም ነበር ትላለች።

"እናትነት ጤንነቴን፣ ጊዜዬን፣ ገንዘቤን፣ ጉልበቴን እና ሰውነቴን ነጥቆታል" ትላለች። "ዋጋው በጣም ውድ ነው፤ የሚከፈለውም ለዘላለም ነው።"

በ40ዎቹ ዕድሜ ውስጥ የምትገኘው አስተማሪዋ ካርመን እናት በመሆናቸው ከሚጸጸቱ ሴቶች መካከል ነች።

ይህ ጸጸት አልፎ አልፎ ነው የሚነገረው። ይህንን ስሜታቸውን ያጋሩን ሴቶች ቤተሰቦቻቸው ስለማያውቁ ሊኖር የሚችለውን ከባድ መዘዝ በመፍራት ስማቸው እንዲገለጽ አይፈልጉም።

ካርመን ከጥቂት ዓመታት በፊት በተደረገ የወላጆች መድረክ ላይ ጸጸቷን በቃላት ገልጻለች። አንዳንድ ሰዎች ርህራሄ ቢያስይዋትም ሌሎች ደግሞ "አስፈሪ" እና "ጭራቅ" እንደሆነች አድርገው ስለዋታል።

ካርመን "እናትነት ባንፈልገው እንኳ የሚከተለን እና የምናከናውነው ማለቂያ የሌለው ሥራ ነው፣ ምክንያቱም ልጆቻችን በእኛ ላይ ጥገኛ ናቸው… የማናመልጠው ወጥመድ ይመስላል" ትላለች።

እናት መሆን ምን ያህል "አስከፊ" እንደሆነም ያለማመንታት ትናገራለች። ስለልጇ ስትጠየቅ ግን ድምጸቷ ጭምር ብሩህ ይሆናል።

"ቲዮ ከጸጸቴ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም። ድንቅ፣ የሚያምር ልጅ ነው። በጣም እወደዋለሁ" ትላለች። "ያለጥርጥር ሕይወቴን ለእሱ እሰጣለሁ። ደግ፣ ቀላል እና ጎበዝ ተማሪ ነው።"

"ብዙውን ጊዜ ሴቶች ስለእናትነታቸው ጸጸታቸውን ለመናገር የሚደፍሩ ከሆነ ይህ የሚመጣው ከፍቅር እጦት ሳይሆን ከመገለል፣ ከድካም ወይም ከጠፋ ማንነት ስሜት ነው" ይላኡ የሥነ-ልቦና ባለሙያዋ አና ማቱር።

ለካርመን "ጥሩ ዜጋ፣ መልካም እና ደስተኛ ሰው" ማሳደግ ትልቅ ኃላፊነት ነው። ይህም ኃላፊነቷን ከባድ ያደርገዋል።

ቲዮ እንደ ትልቅ ሰው እንዲቆጥራት በጭራሽ እንደማትፈልግ ካርመን ለራሷ ቃል ገብታለች። ከድሃ ቤተሰቦች የተገኘችው ካርመን ቤተሰቧም ጥሩ አልነበረም። "ጉልበት ዋና ቋንቋ የነበረበት" ቤት ሲሆን ፍቅር የማግኘት ስሜት ተሰምቷት አታውቅም።

መጀመሪያ ላይ እናት መሆን "የሚያስደስት" ነበር ትላለች። ልጇ ጥሩ እንቅልፍ ይተኛ ነበር። በወሊድ ፈቃድ ላይ እያለችም ሕፃን ልጇን በመንከባከብ ያሳለፈቻቸውን ቀናት ትወዳቸው ነበር።

ልጇ ከባድ የዕድገት ውስንነቶች ማሳየት ሲጀምር እና "እያንዳንዱ ቀላል ነገር ወደ ስጋት ሲቀየር" ነገሮች ተቀያሩ ትላላች ካርመን።

"በጣም የጥፋተኝነት ስሜት ተሰማኝ። ሕይወቱም ወደ ማያበራ ግብግብ ይቀየራል በሚል እጨነቅ ነበር።"

በኋላ ላይም ቲዮ ተመርምሮ ካርመን ትፈራው የነበረው ችግር እንደሌለበት ታወቀ። አሁን በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል። ነገር ግን ጭንቀቱ እና የማያቋርጠው ፍርሃት በሽታ እንዳስከተለባት ትናገራለች።

የእናትነት ጸጸትን ከፍቅር ማጣት እና ጥሩ ካልሆነ አስተዳደግ ጋር ማገናኘትተገቢነት ላይ ጥርጣሩ እንዳላቸው ከእናትነት በኋላ የሚፈጠር ጸጸትን የሚመለከት መጽሐፍ የጻፉት የማኅበራዊ ሳይንስ ተመራማሪዋ ኦርና ዶናት ተናግረዋል።

ዶናት ለ23 እናቶች ቃለ መጠይቅ አድርገዋል። ለሁሉም የእናትነት ጸጸታቸው እና ለልጆቻቸው ባላቸው ስሜት መካከል ያለውን ልዩነት አፅንዖት ሰጥተውታል።

ብዙዎቹ በእናትነት እንደተታለሉ ተሰምቷቸዋል። ምክንያታቸው ደግሞ እውነታው እና ማኅበረሰቡ ለእነሱ ከሰጣቸው ሃሳባዊ እናትነት ጋር ስለማይጣጣም ነው።

"ልጆች በመውለዴ እና እናት በመሆኔ ተጸጽቻለሁ፤ ነገር ግን ልጆቼን እወዳቸዋለሁ... መኖራቸውን ብፈልገውም ግን እናት መሆንን አልፈልግም" ስትል በጥናቱ ውስጥ የተሳተፈች አንዲት የሁለት ታዳጊዎች እናት ተናግራለች።

ያለው መረጃ አነስተኛ ቢሆንም ይህ ያልተለመደ ስሜት እንዳልሆነ ያሳያል። በ2023 በፖላንድ የተካሄደ አንድ ጥናት እንደሚያሳየው ከ5 እስከ 14 በመቶ የሚሆኑ ወላጆች ልጅ በመውለድ ውሳኔኔያቸው ይጸጸታሉ። በድጋሚ ዕድሉን ቢያገኙ ልጅ አለመውለደንም ይመርጣሉ።

ወላጆች ስለጸጸቱ በግልጽ ላይናገሩ ቢችሉም ግን በበይነ መረብ ላይ ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸውን ሰዎች እያገኙ ነው።

ካርመን ከመላው ዓለም 96 ሺህ አባላት ያሉት ልጅ በመውለቸዳው የተጸጸቱ ወላጆች ያሉበት የፌስቡክ ቡድንን ስትቀላቀል ብቻዋን እንዳልሆነች ተገነዘበች።

"እናትነት በጣፋጭ ጊዜያት የተሞላ ነው። ላገኝ እችል የነበረውን ነፃነት ግን አያካክሱም" ስትል ከአምስት ዓመት ልጇ ጋር በአውስትራሊያ የምትኖር አንዲት የቡድኑ አባል የሆነች እናት ለቢቢሲ ተናግራለች።

"በልጄ ዙሪያ ስሆን ጭምብሌን በደንብ እለብሳለሁ" ትላለች። ነገር ግን ወደ አልጋዋ ስትሄድ እና እኔ እና ባለቤቴ አብረን አጭር ግን ጥሩ ጊዜ ሲኖረን ጭምብሌ ይወልቅ እና ብቻዬን መሆንን እመርጣለሁ።"

ልጅ መውለድ ማለት የ

📌 Kaynak

Bu özet BBC Amharic kaynağından otomatik derlenmiştir. Tamamı için orijinal habere gidin.

Orijinal haberi oku →
← Tüm haberlere dön